Thursday, November 22, 2012

ወደ ፍ/ቤት ሽማግሌ ይላካል አይላክም በሚል «አባ» ሳሙኤልና ጠበቆቻቸው ሳይስማሙ ቀሩ


ምንጭ:- አባ ሰላማ ብሎግ
Wednesday, November 21, 2012


የአባ ሚካኤል አስከሬን ወጥቶ እንዲመረመር ፍርድ ቤት ከወሰነ ወዲህ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገቡትና ነገሩን በሽማግሌ ለመጨረስ እየተንቀሳቀሱ ያሉት «አባ» ሳሙኤል ወደ /ቤት ይሄዱልኛል ያሏቸውን ሽማግሌዎች ያዘጋጁ ቢሆንም በጠበቆቻቸው በኩል ግን ሀሳቡ ተቀባይነት ሳያገኝና ሽማግሌም ሳይላክ መቅረቱ ተነግሯል፡፡ በጠበቆቹ በኩል የቀረበው ሐሳብ ተገቢነት ያለውና ህጋዊውን መንገድ የተከተለ  ሲሆን፣ «አባ» ሳሙኤልን «እርስዎ ጳጳስ ሆነው የሽምግልና ሕግን እንዴት አያውቁም? ሽምግልና እኮ እየተካሰሱ ባሉት ሁለት ወገኖች መካከል የሚከናወን የእርቅ ሂደት እንጂ ከፍርድ ቤት ጋር አይደለም፡፡ በፍ/ቤት ሕግ እንዲህ አይነት ሽምግልና ተሰምቶም ታይቶም አያውቅም» ብለዋቸዋል ተብሏል፡፡ አክለውም «ሽማግሌ መላክ ካለብንም መላክ የምንችለው የአባ ሚካኤል ልጅ ነኝ ወደሚለው ወደ ዮሐንስ ነው፡፡» ብለዋል፡፡

ይህን መቀበልና ከዮሐንስ ጋር ያላቸውን የክስ ሂደት በሽማግሌ መጨረስ ሽንፈትና ሞት መሆኑን የተረዱት «አባ» ሳሙኤል ግን ሐሳቡን መቀበል አልፈለጉም፡፡ ምክንያቱም ነገሩን በሽማግሌ መጨረስ የሚቻለው ዮሐንስ የአባ ሚካኤል ልጅ መሆኑን በመቀበል መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ለነገሩ በተደጋጋሚ ለመግለጽ እንደሞከርነው አባ ሚካኤል ልጃቸው መሆኑን ሳይክዱ እየረዱ እንዳሳደጉትና ለቁም ነገር እንዳበቁት «አባ» ሳሙኤልም ጭምር የታወቀ ነው፡፡ ይህ ነገር ይፋ መውጣቱ ግን ምእመናን ለጳጳሳት ያላቸው ክብር ግምት እንዲቀንስ የሚያደርግ በመሆኑ ከዮሐንስ ጋር ነገሩን በሽምግልና መጨረስ የማይታሰብ ነገር ነው፡፡ ውሳኔውን መቀበልም በሕግ ፊት የነገሩን እውነተኛነት ማረጋገጥ ነው፡፡ ከሁለቱ ክፉ ምርጫዎች የቱን እንደሚመርጡ የተቸገሩ የሚመስሉት «አባ» ሳሙኤል ሽማግሌ መላክ አለበት በሚለው አቋማቸው እንደጸኑ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እየተናገሩ ነው፡፡ ሳይማሩ የጠመጠሙት «አባ» ሳሙኤል ሽማግሌዎቹን እኔ አዘጋጅቻለሁ እናንተ የፍ/ቤቱን መንገድ ስለምታውቁት መንገዱን አሳዩኝ ብለው በአቋማቸው ቢጸኑም ጠበቆቹ የአባ ሳሙኤል ሀሳብ ከአንድ ጳጳስ የማይጠበቅና ያልተማረ ሰው እንኳን ያስበዋል ተብሎ የማይጠበቅ በመሆኑና /ቤትም በህግ የያዘውን ጉዳይ በህግ አግባብ ከመጨረስ በቀር የተጣላውና የተካሰሰው ወገን ስለማይኖር ሽምግልና የሚባል ነገር ስለማያስተናግድና ሀሳቡ ህጋዊ ባለመሆኑ ውድቅ በማድረግ ሳይተባበሯቸው ቀርተዋል፡፡


በዚህ የተበሳጩት «አባ» ሳሙኤል «እኔ እያመመኝ ነው፤ ዕረፍት ማድረግ አለብኝ» በሚል ወደ ኢየሩሳሌም መሄዳቸው ተሰምቷል፡፡ ምናልባትም በዚህ ሰበብ የፍርዱን የመጨረሻ ውሳኔ ላለማየት በሚል ይሁን ወይም በእርግጥ አሟቸው ለጊዜው የታወቀ ነገር ግን የለም፡፡

No comments:

Post a Comment