Wednesday, May 9, 2012

አባትነት በገንዘብና በፖለቲካ ሲፈተን

ከታዛቢ

ብፁዕ አቡነ አብርሃም  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምአመናን ተለምኖ በተገኘ ገንዘብ የተገዛውን የዲ.. እና አካባቢው መንበረ ጵጵስና /ቤት እንዲያስረክቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወሰነ።

ማኅበረ ቅዱሳን እያለ ራሱን በሚጠራው ድርጅት አቀንቃኝነታቸው  የሚታወቁት  ወጣቱ ጳጳስ አቡነ አብርሃም በአሜሪካ በተለያየ ስቴቶች በተካሄዱ ጉባዔያት አማካይነት ከምእመናን በተሰበሰበ የአሜሪካ ዶላር 265 000.00 የተገዛው መንበረ ጵጵስና በራሳቸው እና በወሮ. ሀረገወይን ስም ለምን ለማዛወር እንደፈለጉ ባይታወቅም መንበረ ጵጵስናው የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ንብረት መሆኑ እየታወቀ አላስረክብም  ማለታቸው በዘመናዊ አነጋገርየመርካቶ ቁጩ  ዐይነት ቢሆንም የኢትዮጵያና የአሜሪካ መንግሥታት እንዲያውቁት  ተደርጎ በአስቸኩዋይ እንዲያስረክቡ ከዚህ በታች አባሪ በሆነው ደብዳቤ መታዘዛቸውን ቤተ ክርስቲያን ገለጸች።

መቼም መስከራም  ሳይጠባእንደሚባለው የዋሽንግተንና አካባቢዋ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል መንበረ ጵጵስናውን በሥርዐት እንዲያስረክቡ በተደጋጋሚ ቢጽፍላቸውም አሻፈረኝ ብለው መንበረ ጵጵስናውን ለማኅበረ ቅዱሳን /ቤት (ደጀ ሰላምና አሃቲ ተዋህዶ ብሎግ ማዘጋጃ) አከራይተው  እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ  ታውቁዋል። አኒህ ጳጳስ እንደሚታወቀው ቀደም ሲል ከመርካቶው  ራጉኤል ቤተ ክርሰቲያን ባካበቱት  (በዘረፉት ቢባልም ሥራቸው ነውና ራሳቸው ይፈሩ!) ገንዘብ .ኤም.. አጠገብ ፎቅ ቤታቸውን ሠርተው ሳያፍሩ ያስመረቁ ሲሆን፣ በቅርቡም በባንክ ሂሣብ የተጠራቀመውን ከዲ. ከወሰዱት  የሀገረ ስብከቱ ገንዘብ እና አቶ አሥራት ከሚባል (የጎጃሙ ባለአውሊ) የተቸራቸውን ብር 400 000.00 በመጨመር  ሁለት ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ገንዘብ ልዩ  ላንድ ክሩዘር ገዝተው -መንፈሳዊ የሆኑ  ተግባራትን ያከናውኑበታል።

ያዳቆነ ሠይጣን ሳያቀስ አይለቅምእንደሚባለው አዋሳ ትኩረታቸውን በማድረግ ለመዛወር የድጋፍ ድምጽ እያሰባሰቡ ነው ይባላል።  የአዋሳ ሕዝበ ክርስቲያን እምነቱን ለመዝባሪ አሳልፎ  እንደማይሰጥ በተደጋጋሚ ያረጋገጠ ነውና ሙከራቸው ፋይዳ እንደማይኖረው ተስፋ እናደርጋለን፣  በሌላ በኩል ማኅበረ ቅዱሳን በአዋሳ የፈጠረውን ችግርና መንግሥት እንዴት እንደፈታው እየታወቀ አባ አብርሃም በጥቅም ለቆሙለት ማኅበረ  ቅዱሳን አዋሳ ላይ ርስቱን ሊያስመልሱለት ቃል የገቡ ይመስላል፣ ግንሞኞ ሆይገደሉን ሳታይእንደሚባለው በዚህ አካሄዳቸው ከማን ጋር እንደሚላተሙ አዙረው ማሰብ አልቻሉም ማለት ነው - ገንዘብ ያውራል ይባል የለ !

ማኅበረ  ቅዱሳን በአሜሪካ ቤተ ክርስቲያንን ተጠልሎ  ምእመናንን እየከፋፈለ የፖለቲካ መሣሪያ እስከማድረስ የሚያደርገው ተልእኮ እንዲቀጥል ለቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ አቅርቤ አቡነ ፋኑኤልን አስነሳለሁ በማለት ገንዘብና ተወካይ ላኩልኝ ባሉት መሠረት ገንዘቡም መልእክተኞችም (ከአሜሪካ አባ ዘሊባኖስና አባ ገብረ ወልድ) መጥተው አባ አብርሃም ቤት በሰሞኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ጳጳሳትን ለመከፋፈል በዱለታ ላይ ይገኛሉ፣ ለተቀደሰ አገልሎት ሊውል የሚገባውን ገንዘብና ጊዜ ጳጳሳትን ለመደለል ሲያባክኑት ዲያብሎስን በመወከል የአድማ ምንጭ ሆነዋል። መቼም በቤተ ክርስቲያናችን የእምነትና ትምህርት ክህነት በገንዘብ አይሸጥም፣ ለአድማ ተግባርም አይውልም። አባ አብርሃም ግን የማኅበረ ቅዱሳንን የአድማ ተልዕኮ ለማጠናከርና የገንዘብ ምንጫቸው እንዳደርቅባቸው፡ -

1. ዶር. መስፍን የሚባለውን ምእመን ለቴነሲ ኪዳነ ምህረት አለቃ፣
2. ብርሃኑ ጎበና ለሜሪላንድና ፔንሲልቫንያ ኪዳነ ምህረት አለቃ፣
3. ቀሲስ ያሬድ /መድኅን ለኦሃዮ ገብርኤል አለቃ፣
4. አቶ በላቸው ወርቁ (ፓርላማ የነበረና ጥገኝነት ጠይቆ የሚኖር) ለኒዮርክ ኪዳነ ምህረት አለቃ፣
5. አቶ ገብረ ወልድ (ድሮ አባ የነበሩ ግን ከተለያዩ ሴቶች ልጆች ያፈሩ) ዳላስ አጠገብ ለሚገኘው ለቨርጂኒያ ራጉኤል አለቃ አድርገው በመሾም ከአባቶች አንዱ ነኝ የሚሉዋትን ቤተ ክርስቲያናቸውን አዋርደዋል፣  ሀረገ ስብከቱንም የፖለቲካ  መናቆሪያ አድርገዋል። ይኽ እንግዲህ መንግሥት ለረጅም ጊዜ በትእግስት ይዞት የነበረውን የሰለፊያንን ጉዳይ በሳቸው ሀገረ ስብከት እንዲጠናከር ሲያደርጉ የት ላይ ለመቆም ፈልገው እንደሆነ ከወዲሁ ሊታይና ሃይ ሊባሉ ይገባል።

እንግዲህ አባ አብርሃም ዋሽንግተን በቆዩበት ጊዜ የግል ሥራቸውን ሲያሳድዱ መደበኛ ሥራቸው የተጎዳ መሆኑ፣ አብያተ ክርስቲንን ለመከፋፈል ሙያው የሌላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ሥልጣነ ክህነት እየሰጡ በመሾም ትርምሱን ለማጠናከር እንደሞከሩ ከአሠሪያቸው /ቤት በተጻፈላቸው ደብዳቤ ላይ ተጠቅሱዋል።  ይች ቤተ ክርስቲያን እንደአባ አብርሃም ያሉ አባቶች የሚመሩዋት ከሆነ ከሀገርም አደጋ  ነውና ቅዱስ ሲኖዶስም ምእመናንም ሊታገሉዋቸው ይገባል።

እግዚአብሔር ለአባ አብርሃም ልብ እንዲሰጣቸው፣ ጤናቸውንም እንዲመልስላቸው እንጸልይላቸዋለን

No comments:

Post a Comment